Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የቻይና ባለሃብቶች የጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክን እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዢዩአን እና የቻይና ባለሀብቶች የጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክን እየጎበኙ ይገኛሉ።

የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አክሊሉ ታደሰ በጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ ኢንቨስት የሚያደርጉ ቻይናውያን ባለሃብቶችን ይዘው ጅማ ከተማ ገብተዋል።

ከጉብኝት መርሐ ግብሩ ባሻገር ባለሃብቶቹ የኢንቨስትመንት ስምምነት የፊርማ ስነ ስርዓት ያከናውናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከኮርፖሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version