Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የወጪ ንግድ ትስስር ለማሻሻል እየተሰራ ነው – ሚኒስቴሩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ከቻይና ጋር ያላትን የወጪ ንግድ ትስስር ለማሻሻል በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የቻይና-አፍሪካ የእውቀት ሽግግር ሲምፖዚየም በቻይና ቤጂንግ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

በመድረኩ የተሳተፉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዴኤታ ካሳሁን ጎፌ÷በቻይና የኢትዮጵያ ምርት ገዢ ከሆኑ ታላላቅ የቅባት እህል ተቀባይ ነጋዴዎች ጋር ፍሬያማ ውይይት መደረጉን አንስተዋል፡፡

ቻይና የኢትዮጵያ ወጪ የግብርና ምርቶችን በመቀበል ቀዳሚ መሆኗን ጠቁመው÷ በሀገራቱ ንግድ ልውውጥ ላይ የተስተዋሉ ማነቆዎችን ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል፡፡

በሚቀጥሉት ወራት ከቻይና ጋር የሚኖው የወጪ ንግድ መሻሻል እንደሚያሳይ እምነታቸው መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

 

 

 

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version