Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሐረሪ ክልል የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራ አከናወነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሐረሪ ክልል የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራ አከናወነ፡፡

በመርሐ-ግብሩ ላይ ÷ በጎ ሥራ ለትውልድ ስንቅ ማስቀመጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብሩቱካን አያኖ ተናግረዋል።

ሚኒስቴሩ ÷ ለትምህርት ቤቶች እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ተማሪዎችም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተደድር ኦርዲን በድሪ በበኩላቸው ÷ በጎ ፈቃድ ለሰው ልጆች የተሰጠ የመልካምነት ማሳያ በመሆኑ ሁሉም በሚችለው አቅም በበጎ ፈቃድ ተግባራት ሊሳተፍ ይገባል ብለዋል።

የትምህርት ቁሳቁስ የተደረገላቸው ትምህርት ቤቶች እና ተማሪዎችም ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱን አመሥግነዋል።

በምንያህል መለሰ

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version