አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሐረሪ ክልል የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራ አከናወነ፡፡
በመርሐ-ግብሩ ላይ ÷ በጎ ሥራ ለትውልድ ስንቅ ማስቀመጥ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብሩቱካን አያኖ ተናግረዋል።
ሚኒስቴሩ ÷ ለትምህርት ቤቶች እና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ ተማሪዎችም የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል፡፡
የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተደድር ኦርዲን በድሪ በበኩላቸው ÷ በጎ ፈቃድ ለሰው ልጆች የተሰጠ የመልካምነት ማሳያ በመሆኑ ሁሉም በሚችለው አቅም በበጎ ፈቃድ ተግባራት ሊሳተፍ ይገባል ብለዋል።
የትምህርት ቁሳቁስ የተደረገላቸው ትምህርት ቤቶች እና ተማሪዎችም ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱን አመሥግነዋል።
በምንያህል መለሰ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!