Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ እየተካሄደ በሚገኘው በአፍሪካ የማዕድን ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በአውስትራሊያ እየተካሄደ በሚገኘው በአፍሪካ የማዕድን ጉባዔ ላይ እየተሳተፈች ነው፡፡

በጉባዔው የማዕድን ሚኒስትር ዴዔታ ሚሊዮን ማቲዎስ የታደሙ ሲሆን ÷ የኢትዮጵያ የማዕድን ሃብትና የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ማብራራታቸው ተገልጿል።

ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በወርቅ ፍለጋና ምርት፣ በነዳጅና በተፈጥሮ ጋዝ ልማት ፣ በማዳበሪያ ምርትና በሌሎችም ዘርፎች እንዲሰማሩ ሚኒስትር ዴዔታው ጥሪ ማቅረባቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

በዘርፉ ለሚሰማሩ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች መንግስት ሁለንተናዊ ድጋፍ እንደሚያደርግም ማረጋገጣቸው ተጠቁሟል።

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version