አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ሞሮኮ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ከ296 ሰዎች በላይ ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል፡፡
6 ነጥብ 8 የሚለካው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋው ካደረሰው የሰው ሕይዎት መጥፋት ባሻገር እስካሁን 153 ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳደረሰም ነው የተገለጸው፡፡
በተጨማሪም ሕንፃዎች ፈርሰዋል፣ የኤሌክትሪክ ኃይል እና የቴሌፎን ኔትዎርክ ለ10 ደቂቃዎች መጥፋቱን ቢቢሲ አስነብቧል፡፡
የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንዳሉት፥ ታዋቁ የቱሪስት መዳረሻ የሆነችውና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበችው ማራካሽ በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት ደርሶባታል፡፡
ከማራካሽ ከተማ በስተደቡብ የሚገኙ አካባቢዎችም የጉዳቱ ሰለባ እንደሆኑም ተገልጿል።
በደረሰው አደጋ የሟቾች ቁጥር ከዚህ ሊያይል እንደሚችልም ነው የተነገረው፡፡
#Morocco #earthquake
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!