Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ በዚህ የሐዘን ወቅት ከሞሮኮ ጎን መቆሟን አስታወቀች

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ መንግስት በሞሮኮ በደረሰው ከባድ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጿል።

አደጋውን ተከትሎም የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው÷ ኢትዮጵያ በዚህ አስቸጋሪ የሐዘን ወቅት ከሟች ቤተሰቦች እና ከሞሮኮ ሕዝብ ጋር እንደምትቆም ገልጿል፡፡

በሬክተር ስኬል 6 ነጥብ 8 የሚለካው በማዕከላዊ ሞሮኮ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ እስካሁን ከ820 በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን የሀገሪቱ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version