አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) እየተከበረ በሚገኘው የትውልድ ቀን በአዲስ አበባ አምስት የመደመር ትውልድ የሕጻናት መጫወቻ እና የወጣቶች ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እየተመረቁ ነው፡፡
ዛሬ በመላ ሀገሪቱ የትውልድ ቀን “ኢትዮጵያ የትውልዶች ድምር” በሚል መሪ ሃሳብ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው፡፡
በመዲናዋም እየተከበረ በሚገኘው የትውልድ ቀን 5 የመደመር ትውልድ የሕጻናት መጫወቻ እና የወጣቶች ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እየተመረቁ መሆኑን ከከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
የሕጻናት መጫወቻ እና የወጣቶች ስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራዎቹ በአምስት ክፍለ ከተሞች ነው እየተመረቀ የሚገኘው፡፡