Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለ2016 አዲስ ዓመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል፡፡

የጋራ ምክር ቤቱ የ2016 አዲስ ዓመት የሠላምና የደስታ እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡

በአዲሱ ዓመት በፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲሁም በመንግስትና በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አብሮ የመሥራት ባሕል የሚዳብርበትን ሁኔታ ለመፍጠር በትብብር እንደሚሰራ አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም የፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ አስቻይ ሁኔታ የሚፈጠርበትን የፖለቲካ ምኅዳር ለማመቻቸት የተቻለውን ሁሉ እንደሚያደርግ ነው የጠቀሰው፡፡

“አዲሱ ዓመት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ሠላምና መረጋጋት የሚፈጠርበት የሠላም፣ የደስታና ተድላ ዓመት ይሁን” ሲልም መልካም ምኞቱን ገልጿል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version