አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ)በሱዳን የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ኦማር በሽር ማኒስ የተመራ ከፍተኛ የልኡካን ቡድን ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገብቷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸውም ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ በመገኘት ለልኡካን ቡድኑ አቀባበል አድርገዋል።
የልኡካን ቡድኑ ነገ እና እሁድ በሁለቱ አገራት መካከል በሚካሄደው መደበኛ የድንበር ጉዳዮች ከፍተኛ የፖለቲካ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ እንደሚሳተፍ ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

