አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌደራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ዶ/ር) ከዓለም የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ) የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ክትትል ልዑካን ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷በኢትዮጵያ እየተከናወነ በሚገኘው የፀረ-ሙስና ትግል ዙሪያ በትኩረት መክረዋል፡፡
በቀጣይም የፀረ-ሙስና ትግሉን ለማጠናከር በትብብር በሚሰሩ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡