Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ለስደተኞች የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ለመስጠት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለስደተኞች የዲጂታል ፋይዳ መታወቂያ ለመስጠት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ፊርማ ዛሬ በሶስት ተቋማት መካከል ተፈርሟል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢፌዴሪ ስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት፣ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጽህፈት ቤት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን ናቸው።
በስምምነቱ አማካኝነት ስደተኞች በዲጂታል መታወቂያው በኢትዮጵያ የሚሰጡ የተለያዩ አገልግሎቶችን ማግኘት እንደሚችሉ መገለፁን ኢዜአ ዘግቧል።
ተቋማቱ የጋራ የመረጃ ልውውጥ እንደሚያደርጉና ስምምነቱም ኢትዮጵያ ለስደተኞች ያላትን በጎ አመለካከትና ተቀባይነት የሚያሳይ ነው ተብሏል።
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version