Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከንቲባ ከድር ጁሀር ለኢሬቻ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር የሰላም፣ የፍቅር፣ የእርቅ፣የወንድማማችነት፣ የእህትማማችነትና የአንድነት ማሳያ ለሆነው የኢሬቻ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል።

የተለያዩ የባህል ክንውን የሚከናወንበት የእሬቻ በአል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል።

በአሉ የሰላም የደስታ እንዲሆን መልካም ምኞታቸውን በመግለፅ በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንዲጠናቀቅ እና አንዱ አንዱን የሚያግዝበትና ሌሎች ተሞክሮዋችን የምንካፈልበት ከመሆኑም በተጨማሪ አብሮነትንና መተባበርን የሚያጎለብት ታላቅ በዓል ነው ሲሉ መግለፃቸውን ከከተማው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version