Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያና ኖርዌይ በደን ልማት አስተዳደር ላይ በትብብር ለመስራት ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ከኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክሪስተንሰን ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ኢትዮጵያ እና ኖርዌይ በግብርናው ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

በተለይም በዘላቂ ደን ልማት አስተዳደር ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ በማልማት ላይ በትብብር በቅንጅት ለመስራት ተወያይተዋል፡፡

በተጨማሪም የዜጎችን ሕይወት ማሻሻል በሚያስችሉ የምግብ ስርዓት ትራንስፎርሜሽን ግቦች ዙሪያ መምከራቸውን አምባሳደሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

Exit mobile version