አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የትምህርት ሚኒስትር አህመድ ቤልሁ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ውይይቱ በፓሪስ እየተካሄደ ከሚገኘው 42ኛው የዩኔስኮ ጠቅላላ ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ነው የተደረገው፡፡
በዚህም የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የሰጠችውን ነጻ የትምህርት ዕድል፣ በዩኒቨርስቲዎች ራስ ገዝ አስተዳደር ተግባራዊነት እና በትምህርት መሰረት ልማት ዙሪያ መክረዋል፡፡
በቀጣይም የሁለቱ ሀገራት የትምህርት ትብብር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሚኒስትሮቹ በአዲስ አበባና በአቡዳቢ ተገናኝተው ለመወያየት መስማማታቸውን በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
#Ethiopia #UAE #France #UNESCO
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!