አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በተለይም በተለዩ የትምሕርት መስኮች ላይ የውጭ ልምድ እንደሚያስፈልጋት የትምሕርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የትምሕርት ሚኒስትር እና የዩኔስኮ ብሔራዊ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት – ዓለም አቀፍ የትምሕርት ቢሮ (ዩኔስኮ- አይቢኢ) ቦርድ ፕሬዚዳንት ስቪን ኦስትቬት ጋር በፈረንሳይ ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም÷ የኢትዮጵያን የትምሕርት ሥርዓት ለማሻሻል እና ለማዘመን የተከናወኑና በመተግበር ላይ ያሉ የለውጥ ተግባራትን ሚኒስትሩ አብራርተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በተለይም በዘርፉ በተለዩ የትምሕርት መስኮች የውጭ ልምድ እንደሚያስፈልጋት በአጽንኦት መግለጻቸውን የትምሕርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡
የዩኔስኮ-አይቢኢ የቦርድ ፕሬዚዳንት በበኩላቸው÷ በኢትዮጵያ የትምሕርት ሥርዓቱን በአዲስ መልክ ለማሻሻልና ለማዘመን የተከናወኑ ሥራዎችን አድንቀዋል፡፡
ቢሮውም የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!