Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያ በተለዩ የትምሕርት መስኮች የውጭ ልምድ ያስፈልጋታል – ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በተለይም በተለዩ የትምሕርት መስኮች ላይ የውጭ ልምድ እንደሚያስፈልጋት የትምሕርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

የትምሕርት ሚኒስትር እና የዩኔስኮ ብሔራዊ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት – ዓለም አቀፍ የትምሕርት ቢሮ (ዩኔስኮ- አይቢኢ) ቦርድ ፕሬዚዳንት ስቪን ኦስትቬት ጋር በፈረንሳይ ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ የኢትዮጵያን የትምሕርት ሥርዓት ለማሻሻል እና ለማዘመን የተከናወኑና በመተግበር ላይ ያሉ የለውጥ ተግባራትን ሚኒስትሩ አብራርተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በተለይም በዘርፉ በተለዩ የትምሕርት መስኮች የውጭ ልምድ እንደሚያስፈልጋት በአጽንኦት መግለጻቸውን የትምሕርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

የዩኔስኮ-አይቢኢ የቦርድ ፕሬዚዳንት በበኩላቸው÷ በኢትዮጵያ የትምሕርት ሥርዓቱን በአዲስ መልክ ለማሻሻልና ለማዘመን የተከናወኑ ሥራዎችን አድንቀዋል፡፡

ቢሮውም የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version