Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በቻይና ብሔራዊ ኮንግረስ ምክትል ሊቀ መንበር የተመራ ልዑክ አዲስ አበባ ገባ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና ብሔራዊ ኮንግረስ ምክትል ሊቀ መንበር ሎሳንግ ጂያልትሰን የተመራ የልዑካን ቡድን ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብቷል፡፡

የልዑካን ቡድኑ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ ታገሰ ጫፎ አቀባበል አድርገውለታል።

ልዑኩ በቆይታው ከምክር ቤት አባላትና ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት እንደሚያደርግ ይጠበቃል ሲል አዜአ ዘግቧል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version