Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በአራቱም የጎጃም ዞኖች የሰላም ሁኔታ ከፍተኛ መሻሻሎች እያሳየ መሆኑ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በአራቱም የጎጃም ዞኖች እና ወረዳዎች ያለው የሰላም ሁኔታ ከፍተኛ መሻሻሎች እያሳየ መሆኑን ኮማንድ ፖስቱ አረጋገጠ።

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት የዕቅድ አፈጻጸሙን በደብረማርቆስ ከተማ በገመገመበት ዕለት እንደተገለጸው ፥ በጎጃም ባሉ ሁሉም ዞኖችና ከተሞች በተሰራው ህግ የማስከበር ስራ ለውጥ ታይቷል ።

በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተደድር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰው እንዲሁም የምስራቅ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሐመድ ተሰማ እንደተናገሩት ፥ ሠራዊቱ በተሰማራባቸው ሁሉም አካባቢዎች የመንግስት መዋቅር መልሶ እየተደራጀ ነው።

ፖሊስ ፣ ሚሊሻ እና ሌሎች አካላት ከመከላከያ ጋር ተሰልፈው ግዳጅ እየተወጡ እንደሚገኙ መገለጹን ከመከላከያ ሠራዊት የማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

በተጨማሪም የጽንፈኛው ቡድንም ከህዝብ እየተነጠለ መጥቷል ፤ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማትም ስራ ጀምረዋል ተብሏል ።

የውይይቱ ተሳታፊዎች ሰላሙ ቀጣይ እንዲሆን የፖለቲካ አመራሩ የህዝብ ግንኘነት ስራ በማጠናከር ፣ የፖሊስ ፣ የሰላም ማስከበር እና የሚሊሺያ አባላትን በማደራጀት ፣ የህዝብ አገልግሎትን በተደራጀ መንገድ በመምራት ከሠራዊቱ ጎን በመሆን የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ ማረጋገጣቸውም ተገልጿል ።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version