Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ተመድና ብሪክስ በእስራዔል-ሃማስ ጦርነት ላይ ሊወያዩ ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) እና የብሪክስ አባል ሀገራት በእስራዔል-ሃማስ ጦርነት ላይ ሊወያዩ መሆኑ ተገለጸ።

በውይይቱ የሩሲያውን ፕሬዚዳንት ቭላድሜር ፑቲን እና የቻይናው አቻቸውን ሺ ጂንፒንግ ጨምሮ የተመድ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ይካፈላሉ ተብሏል፡፡

በበይነ-መረብ በሚካሄደው በዚህ ውይይት የብሪክስ አባላቱ መሪዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪም በመጪው ጥር በይፋ ብሪክስን ይቀላቀላሉ የተባሉት ሀገሮች እንደሚሳተፉ ተነግሯል።

የውይይት መድረኩን የወቅቱ የብሪክስ ሊቀመንበር የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ እንደሚመሩት የተጠቆመ ሲሆን በጋዛ ባለው ሰብዓዊ ቀውስ ላይ ተነጋግረው የጋራ መግለጫ እንደሚያወጡ ተነግሯል።

#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version