Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በሲዳማ ክልል ከ336 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለሚገነቡ ፕሮጀክቶች የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ

 

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሲዳማ ክልል ከ336 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በ8 ወረዳዎች ለሚገነቡ የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሂዷል።

የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተደድር ደስታ ሌዳሞ በጎርቼ ወረዳ በ41 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር የሚገነባውን የ”ሶካ ሶኒቾ አሳራዶ ዳማ” የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ሥራ አስጀምረዋል።

የሶካ ሶኒቾ አሳራዶ ዳማ ፕሮጀክት በሁለት ቀበሌዎች የሚኖሩ 7 ሺህ 200 የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑም ታውቋል።

የውሃ ፕሮጀክቶቹ በክልሉ መንግስት በጀት እና በአጋር አካላት አማካኝነት የሚከናወኑ መሆናቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

Exit mobile version