Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የብሪክስ ሀገራት ዳኞች ሴሚናር በቻይና እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከብሪክስ ሀገራት የተወጣጡ ዳኞችን ያካተት ሴሚናር በቻይና ቤጂንግ እየተካሄደ ነው፡፡

በሴሚናሩ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ፉአድ ኪያር የተመራ የሶስቱም የፌዴራል ፍ/ቤቶች ልዑክ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡

በመድረኩ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ የብራዚልና የግብጽ ዳኞችን ጨምሮ ከሀገራቱ ፍትሕ ሚኒስቴር የተወከሉ ከፍተኛ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል፡

በኢትዮጵያም ከፍትሕ ሚኒስቴር የተወከሉ ዓቃቤያን ሕጎች እየተሳተፉ መሆኑን የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት መረጃ ያመለክታል።

Exit mobile version