Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የአፍሪካ ወጣቶች ወር የማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዘንድሮ ለ16ኛ ጊዜ የተከበረው የአፍሪካ ወጣቶች ወር የማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሄደ።

የማጠቃለያ መርሐ ግብሩ “ድንበር ተሻጋሪ የወጣቶች እንቅስቃሴ ለፓን-አፍሪካኒዝም“ በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ እንደሚገኝ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በየዓመቱ በፈረንጆቹ ህዳር ወር ሙሉውን የሚከበረው የአፍሪካ የወጣቶች ወር የአህጉሩን ወጣቶች ስብዕና ከመገንባት ጀምሮ ሌሎች ወጣቱን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ጉዳዮች ትኩረት ተሰጥቷቸው ውይይት ማድረግን ጨምሮ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል።

የአፍሪካ ወጣቶች ወር ሲከበር የወጣቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት በተጨባጭ ለመተግበር የሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም ይመከራል።

Exit mobile version