አዲስ አበባ፣ ሕዳር 25፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን በዐርባ ምንጭ ከተማ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ ወደ ዐርባ ምንጭ ከተማ ያቀኑት÷ “ከእዳ ወደ ምንዳ” በሚል መሪ ሐሳብ በተዘጋጀው 4ኛ ዙር የመንግሥት አመራሮች የዐቅም ግንባታ ስልጠና ላይ ማጠቃለያ ለመስጠት ነው፡፡
ከስልጠናው ማጠቃለያ ጎን ለጎንም በዐርባምንጭ ከተማ የሚገኙ የተፈጥሮ ደን እንዲሁም የዓዞ እርባታ ማዕከልን እና የተለያዩ የልማትና የመስኅብ ሥፍራዎችን ጎብኝተዋል።
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!