Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በሕንድ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀናቸው

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕንድ በተካሄደ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡

ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በሕንድ ኮልካታ ከተማ የተካሄደውን የ25 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በቀዳሚነት አጠናቅቃለች፡፡

አትሌቷ ርቀቱን 1ሰዓት 18 ደቂቃ ከ47 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ቀዳሚ የሆነቸው ፡፡

በውድድሩ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው ሁለተኛ ደረጃ መያዟን ከታታ ስቲል ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪም በተመሳሳይ የሩጫ ውድድር በወንዶች ዘርፍ አትሌት ተስፋዬ ደመቀ ሦስተኛ በመውጣት አጠናቅቋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version