Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የምሥራቅ አማራ ኮማንድ ፖስት የሰላምና ጸጥታ ሥራዎችን አፈጻጸም እየገመገመ ነው

አዲስ አበባ፣ ታኅሣስ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የምሥራቅ አማራ ኮማንድ ፖስት የሰላምና ጸጥታ ሥራዎችን አፈጻጸም በኮምቦልቻ ከተማ እየገመገመ ነው፡፡

ኮማንድ ፖስቱ በወቅታዊ የአካባቢው ሰላምና ደኅንነት ሁኔታዎች ላይ ግምገማ እያካሄደ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የግምገማውን መጠናቀቅ ተከትሎም የቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተመላክቷል፡፡

በግምገማ መድረኩ ላይ የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴንን ጨምሮ የኮማንድ ፖስቱ አመራሮችና ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version