Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ኢትዮጵያና ፈረንሳይ በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ በጋራ መስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የመከላከያ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

ሚኒስቴሩ ከፈረንሳይ ፓርላማ የመከላከያ ጉዳዮች ኮሚቴ አባላት ጋር በጋራ ለመስራት በሚያስችል መልኩ ውይይት መደረጉን ውይይቱን የተካፈሉት የመከላከያ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ኃላፊ ብርጋዲየር ጄኔራል ወርቁ ከበደ ገልፀዋል፡፡

የመከላከያ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) የልዑካን ቡድኑን ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት÷ በፈረንሳይና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት ረጅም አመታትን ያስቆጠረ ታሪካዊ ግንኙነት መሆኑን ብርጋዲየር ጄኔራል ገልፀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከፈረንሳይ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት አጠናክራ ለመቀጠል ፍላጎት እንዳላት አብርሃም በላይ (ዶ/ር) መግለፃቸውን ከመከላከያ ሠራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

አብርሀም በላይ (ዶ/ር) አባላቱ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ባደረጉት ውይይት ደስተኛ መሆናቸውንና የኢትዮጵያ መከላከያ ከፈረንሳይ መንግስት ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኑንም ገልጸዋል ተብሏል፡፡

የፈረንሳይ ፓርላማ የመከላከያ ጉዳዮች ኮሚቴ አባላትን የወከሉት ቶማስ ጋሲሎይድ÷ ከመከላከያ ሚኒስትሩ ጋር ባደረጉት ውይይት በቀጣናዊ በአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ትብብሮች ዙሪያ መምከራቸው ተገልጿል፡፡

እንዲሁም በሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ በሰው ሃይል ግንባታና ድጋፍ አብሮ ለመስራት የሚያስችል ውይይት ማድረጋቸውን ተጠቅሷል፡፡

 

 

Exit mobile version