Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከዓድዋ ድል ጋር የተያያዙ ቅርሶች ለአዲስ አበባ ከተማ ተበረከተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተለያዩ ወረዳዎች የሰበሰባቸውን ከዓድዋ ድል ጋር የተያያዙ ቅርሶች ለአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር አስረከበ፡፡

ቅርሶቹንም የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ምስኪያ አብደላ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤትና የካቢኔ ጉዳዮች ኃላፊ ጥላሁን ወርቁ አስረክበዋል፡፡

አሥተዳደሩ ያቀረበውን ጥሪ ተቀብሎ ከዓድዋ ድል ጋር የተያያዙ ቅርሶችን በማበርከቱም አቶ ወርቁ ለክልሉ ምስጋና ማቅረባቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡

Exit mobile version