አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በሁሉም ዞኖች በሚገኙ 20 ከተሞች በነገው ዕለት ሕዝባዊ ውይይት ይካሄዳል፡፡
በውይይት መድረኩ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከሕብረተሰቡ ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ለውይይት መድረኩም የተለያዩ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ወደ ከተሞቹ እየገቡ መሆኑን በብልጽግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

