Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ሕዝባዊ ውይይቶችን ለመምራት ሠመራ ገቡ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በነገው ዕለት “ኅብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ለዘላቂ ሰላምና ሁለንተናዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ሐሳብ በ20 ከተሞች ሕዝባዊ ውይይቶች ይካሄዳሉ፡፡

በአፋር ክልል የሚካሄደውን ሕዝባዊ ውይይት ለመምራትም የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ዛሬ ሠመራ ገብተዋል፡፡

አመራሮቹ በሠመራ ሱልጣን አሊ ሚራሕ ሀንፍሬ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የአፋር ክልል አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

በክልሉ በሠመራ እና አሳዒታ ከተሞች ሕዝባዊ የውይይት መድረኮች እንደሚካሄዱ ተገልጿል፡፡

በታሪኩ ወ/ሰንበት

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version