Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የተለያዩ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች አዲስ አበባ ገቡ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቦትስዋና፣ የኮትዲቯር፣ የላይቤሪያ እና የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በ44ኛው የአስፈፃሚዎች ስብሰባ ላይ ለመካፈል ማምሻውን አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

የቦትስዋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለሞጋንግ ክዋፔ (ዶ/ር) እና የኮትዲቯር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አዶም ካኩ አዲስ አበባ መግባታቸው ተመላክቷል፡፡

እንዲሁም የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳራ ቤይሶሎ ያንቲ እና የቤኒን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አውሪሊየን አግቤኖንቺ አዲስ አበባ ገብተዋል፡

Exit mobile version