አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ከኖርዌይ የዓለም አቀፍ የልማት ትብብር ሚኒስትር አኔ ቤዝ ቲቭነሪም ጋር በሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያዩ፡፡
ሁለቱ ሚኒስትሮች ባደረጉት ውይይት ፥ በአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ በደን ልማት፣በትምህርት ፣ በግብርና ዘርፍ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።
አምባሳደር ታዬ በዚህ ወቅት ፥ ኖርዌይ በሁኔታዎች የማትቀየር የኢትዮጵያ ጠንካራ ወዳጅ ሀገር መሆኗን ገልፀዋል።
ሚኒስትር አኔ ቤዝ ቲቭነሪም በበኩላቸው ፥ ኖርዌይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የቆየ ጠንካራ ግንኙነት አጠናክራ እንደምትቀጥል ም ነው የተናገሩት፡፡
ሚኒስትሮቹ ሁለቱ ሀገራት በትብብር በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
#Ethiopia
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!