Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ቤኒን በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ልምድ መቅሰም እንደምትፈልግ ገለጸች

አዲስ አበባ፣ የካቲት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ቤኒን በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ልምድ መቅሰም እንደምትፈልግ ገለጸች፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ከቤኒን አቻቸው ኦሉሸጉን ባካሪ ጋር ተወያይተዋል።

አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ፥ ቤኒን በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት ማድነቃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ኦሉሼጉን ባካሪ በበኩላቸው ፥ ቤኒን በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ከኢትዮጵያ ልምድ መቅሰም ትፈልጋለች ብለዋል።

ሚኒስትሮቹ የፖለቲካ ግንኙነቶችን ወደ ኢኮኖሚያዊ ትብብር ለማሳደግ ትክክለኛው ጊዜ አሁን እንደሆነም ነው የተስማሙት፡፡

Exit mobile version