Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስና ንግድ ባንክ አሸንፈዋል

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ15ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ላይ ከሲዳማ ቡና ጋር የተገናኙት ፈረሰኞቹ በአማኑኤል ተርፉ ብቸኛ ጎል 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ውጤቱን ተከትሎም ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥቡን 28 አድርሷል።

ምሽት 12 ሰዓት በተከናወነ ሌላ ጨዋታ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፋሲል ከነማን 4 ለ 2 በማሸነፍ የሊጉን መሪነት ከመቻል በጊዜያዊነት ተረክቧል፡፡

Exit mobile version