Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የአፍሪካን እምቅ ሃብት መጠቀም በአባል ሀገራቱ መካከል የዳበረ ትብብርና የወንድማማችነት እሴት ይፈልጋል – ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ የካቲት 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ አህጉርን እምቅ ሃብት መጠቀም በአባል ሀገራቱ መካከል የዳበረ ትብብር እና የወንድማማችነት እሴት ይፈልጋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ፥ ከቡሩንዲ፣ አንጎላ፣ ሞዛምቢክ እና ናይጄሪያ ፕሬዚዳንቶች ጋር የጋራ የልማት ጥረቶችን የተመለከቱ የሁለትዮሽ ውይይቶች ማካሄዳቸውን ገልጸዋል፡፡

“የአህጉራችንን እምቅ ሃብት መጠቀም በአባል ሀገራት መካከል የዳበረ ትብብር እና የወንድማማችነት እሴት ይፈልጋል” ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

Exit mobile version