Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አቶ እንዳሻው ጣሰው ሠላምን ለማፅናት ዘብ መቆም እንደሚገባ አስገነዘቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው የሁላችንም ጉዳይ የሆነውን ሠላምን ለማፅናት ዘብ መቆም አለብን ሲሉ አስገነዘቡ፡፡

ርዕሰ መሥተዳድሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ የሠላም ጉዳይ የሁላችንም ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡

የሁላችንም ጉዳይ የሆነውን ሠላምን ለማፅናትም ዘብ መቆም አለብን ነው ያሉት፡፡

በሠላም መደፍረስና በግጭት ጥቂቶች ጊዜያዊ ጥቅም ያገኙ ሊመስላቸው እንደሚችል ጠቁመው÷ ነገር ግን ሠላም ለዘላቂ የጋራ ዕጣፈንታችን መልካም መሆን እጅግ መሠረታዊ እሴት ነው ሲሉ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም ለሠላም ግንባታና ለሠላም እሴቶች መጠናከር በጋራ በመሥራት ኃላፊነታችንን መወጣት ይኖርብናል ብለዋል በመልዕክታቸው፡፡

Exit mobile version