Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 46 በርሚል ነዳጅ ተያዘ

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 46 በርሚል ነዳጅ መያዙን የሚዛን አማን ከተማ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር አዳነ አለማየሁ እንደገለጹት÷ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ ከተያዘው ነዳጅ ውስጥ 35 በርሚሉ ናፍታ ሲሆን 11 በርሚሉ ደግሞ ቤንዝል ነው፡፡

በተሽከርካሪ ተጭኖ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ በተያዘው ነዳጅ ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የሕገ-ወጥ ነዳጅ ግብይት መበራከት የግብይት ሥርዓቱን ከማወክ ባለፈ በህብረተሰቡ ዘንድ የቅሬታ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን አንስተዋል፡፡

በቀጣይ ማደያዎች በመንግስት ድጎማ የሚመጣው ነዳጅ ላይ የሚያደርጉትን ሕገ-ወጥ ግብይት በማቆም በተቀመጠው አሰራር መሰረት ጤናማ የግብይት ሒደት እዲከተሉ አስገንዝበዋል፡፡

ደንቡን በሚጥሱት ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ማረጋገጣቸውንም የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version