Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከንቲባ ከድር ጁሃር የትንሳኤ በዓልን በመደጋገፍ ማክበር እንደሚገባ ገለጹ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትንሳኤ በዓልን ስናከብር የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህላችንን በማጠናከር ሊሆን ይገባል ሲሉ የድሬዳዋ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ገለጹ።

ከንቲባው ለትንሳኤ በዓል ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መልዕክት÷ ለክርስትና ሐይማኖት ተከታዮች በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የደስታ እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡

በዓሉን ስናከብርም ለችግር የተዳረጉ ሕጻናትና አረጋውያንን በመርዳት ሊሆን ይገባል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የሰላም፣ የአንድነትና የልማት ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል።

Exit mobile version