Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

1 ሺህ 181 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶስት ዙር በተከናወነ በረራ በሳዑዲ ዓረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 181 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

ከተመላሾች ውስጥ 1 ሺህ 139 ወንዶች፣ 25 ሴቶች፣ 17 ጨቅላ ህጻናት እና 6 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡

ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ሥራ እየተከናወነ መሆኑንም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

 

Exit mobile version