አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ የ9 ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማና የመጪው የክረምት ስራዎች ትውውቅ መድረክ በጎንደር ከተማ መካሄድ ጀምሯል።
መድረኩ “የዲሞክራሲ እሴት እና ባህል ለብልፅግናችን” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ መሆኑን የዘገበው ኢዜአ ነው።
በመድረኩ የብልፅግና ፓርቲ የዋናው ጽህፈት ቤት የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ፣ የፓርቲው የወጣቶችና ሴቶች ሊግ አመራሮችና ሌሎች የፌደራልና የክልል የብልፅግና ፓርቲ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ አመራሮች ተገኝተዋል።