Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ም/ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ከከምባታ ዞን ወጣቶች ጋር እየመከሩ ነው

 

አዲስ አበባ፣ ግንቦት10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው ከከምባታ ዞን ወጣቶች ጋር በሰላምና በልማት ጉዳዮች ላይ በዱራሜ ከተማ እየተወያዩ ነው፡፡

በውይይት መድረኩ ከምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ ሌሎች የክልሉና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ከዞኑ የተውጣጡ ወጣቶች ተገኝተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ከከምባታ ዞን ወጣቶች ጋር በሰላም፣በልማት እና በመልካም አስተዳደር ጉዳዮች ላይ እየተወያዩ እንደሆነ ከክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version