Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሣይንስና ፈጠራ ሥራዎች ዐውደ-ርዕይ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሣይንስና ፈጠራ ሥራዎች ዐውደ-ርዕይና ውድድር በሆሳዕና ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡

ዐውደ-ርዕዩ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው በተገኙበት “ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሣይንስ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ” በሚል መሪ ሐሳብ ነው እየተካሄደ የሚገኘው፡፡

ለሁለት ቀናት በሚቆየው ዐውደ-ርዕይ ላይ መምህራን፣ ተማሪዎች እና ኢንተርፕራይዞችን ጨምሮ ከ100 በላይ የፈጠራ ባለሙያዎች እየተሳተፉ ነው፡፡

በፈቲያ አብደላ

Exit mobile version