Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኖሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች በሀገራዊ ስትራቲጂያዊ ጉዳዮች ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር ከተወያዩ በኋላ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡

ችግኝ ተከላው “ኢትዮጵያ ትተክላለች ትውልድ ያፀናል” በሚል መሪ ሐሳብ የተጀመረው የዘንድሮው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር አካል መሆኑ ተገልጿል፡፡

በዚሁ ወቅት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ባስተላለፉት መልዕክት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ለአንድ አካል የሚተው ሳይሆን የሁሉንም ኢትዮጵያውያን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

በቀጣይም በሀገራዊ የልማት መርሐ-ግብሮች ላይ በትብብር እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

Exit mobile version