Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፕሬዚዳንት ፑቲን በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ሃዘን ገለጹ

UKRAINE-CRISIS/PUTIN

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማቸውን ጥልቅ ሃዘን ገልጸዋል፡፡

ፕሬዚዳንቱ ባስተላለፉት የሃዘን መልዕክት÷በአደጋው ቤተሰቦቻቸውን ላጡ ዜጎች መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በፍጥነት እንዲያገግሙ መልካም ምኞታቸውን መግለጻቸውንም በኢትዮጵያ የሩሲያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version