Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ከሱዳን የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ከሱዳን የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ቶም ፔሪሎ ጋር በፅህፈት ቤታቸው ዛሬ ተወያይተዋል።

ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው÷ በአፍሪካ ቀንድ ቀጠናዊ በሆኑ ጉዳዮች እና በተለይም በሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ መክረዋል።

በሱዳን ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማድረግ ላይ ስለሚገኙት ጥረት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለልዩ መልዕክተኛው መግለፃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በወቅቱ በሱዳን ሰላም እና ፀጥታን በዘላቂነት ለማስፈን በጋራ ለመስራት ሁለቱ ወገኖች ተስማምተዋል።

Exit mobile version