Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በአዲስ አበባ ኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3 ሺህ 203 ደርሷል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች 3 ሺህ 203 መድረሱን የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በፌስ ቡክ ገጹ ባወጣው መረጃ በከተማዋ ባለፉት 24 ሰአታት 98 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው አስታውቋል።

በተጨማሪም በአዲስ አበባ በተደረጉ የአስከሬን ምርመራዎች አንድ ሰው ቫይረሱ ተገኝቶበታል ብሏል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ በትናንትናው እለት 79 ሰዎች ከአዲስ አበባ ከኮሮና ቫይረስ አገግመዋል፡፡

Exit mobile version