Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የጋራ መድረክ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር፣ የክልል ጤና ቢሮ እና ተጠሪ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የጋራ መድረክ በድሬዳዋ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር÷ መድረኩ እርስ በርስ ለመማማር፣ ተግባራትን በመገምገም ጥንካሬና ክፍተቶችን ለይተን የቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡

የጤና ሥራ የጋራ በመሆኑ ሁሉም በቅንጅት ከሠራ ውጤታማ መሆን እንደሚቻልም በመድረኩ ተገልጿል፡፡

Exit mobile version