Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

በትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በምሥራቅ ሐረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ ዱርሲቱ ቢሊሱማ ቀበሌ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የሥድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ካሳዬ አበበ እንደገለፁት÷ አደጋው የተከሰተው ከአዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ ይጓዝ የነበረ የነዳጅ ቦቴ ከባድ መኪና ከባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ  ጋር በመጋጨታቸው ነው፡፡

የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

በተሾመ ኃይሉ

Exit mobile version