Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ከዓለም የምግብ ፕሮግራም ተወካይ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) ከዓለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተወካይ ዝላታን ሚሌሲክ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷የዜጎችን ሕይወት ማሻሻል በሚችሉ ፕሮጀክቶች ላይ በትብብር መስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም አነስተኛ የመስኖ ግድብ ፕሮጀክቶችን በዘላቂነት ለማስፋፋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version