Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ብሔራዊ የሲቪል አቪዬሽን ትራንስፎርሜሽን መርሐ-ግብር ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን በአቪዬሽን መስክ ኢትዮጵያን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግራትን ብሔራዊ የሲቪል አቪዬሽን ትራንስፎርሜሽን መርሐ-ግብር ይፋ አደረገ፡፡

የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴዔታ ዳንጌ ቦሩ እንደገለጹት÷ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ መሪነቷን በዘላቂነት ለማስቀጠል ሁሉን አቀፍ ለሆነ የዘርፉ መዘመን ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ነው።

መርሐ-ግብሩ ዘርፉን በላቀ ቴክኖሎጂ የማስቀጠል ትልም እንዳለው ገልጸው÷ በመጪው ጊዜም ቴክኖሎጂን ማዕከል ያደረገ የአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ደኅንነትን የማስጠበቅ ሥራ ይቀጥላል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው መንግሥቴ በበኩላቸው÷ መርሐ-ግብሩ ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፍ ደኅንነት የላቀ ተግባር ለማከናወን ቁርጠኛ መሆኗን የሚያመላክት ነው ብለዋል።

ይህ ትራንስፎርሜሽን እያደገ የመጣውን የአቪዬሽን መስክ መሰረት በማድረግ ዘርፉ የሚጠይቀውን አሁናዊ ቁመና ለመላበስ የሚያስችል መሆኑንም አመላክተዋል፡፡

Exit mobile version