Site icon Welcome to Fana Media Corporation S.C

ከ15 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዙን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከብሄራዊ መረጃና ደኅንነት ጋር በመሆን በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገባ ዕቃ መያዙን ነው ያስታወቀው፡፡

ዕቃዎቹን ወደ አዲስ አበባ በማስገባት ሊያሰራጩ ሲሞክሩ ገላን ኮንዶሚንየም አካባቢ ሹፌሩንና ረዳቱን ጨምሮ የኮንትሮባንዱ ዕቃዎቹ መያዛቸውን የፌደራል ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡

Exit mobile version