Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ማንቼስተር ሲቲ እና ክሪስታል ፓላስ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ15ኛ ሳምንት የኢንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ወደ ሴልሁሩስት ፓርክ ያቀናው ማቼስተር ሲቲ ከክሪስታል ፓላስ ጋር 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል፡፡

በጨዋታው ለክሪስታል ፓላስ ግቦቹን ሙኖዝ እና ላክሮይክስ ሲያስቆጥሩ ለማንቼስተር ሲቲ ደግሞ ኤርሊንግ ሃላንድ እና ሪኮ ልዊስ አስቆጥረዋል፡፡

በተመሳሳይ ሰዓት በተደረጉ ጨዋታዎች አስቶንቪላ ሳውዝአምፕተንን 1 ለ 0 እንዲሁም ብሬንትፎርድ ኒውካስል ዩናይትድን 4 ለ 2 አሸንፈዋል፡፡

ምሽት 2 ሰዓት ከ30 ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ኖቲንግሃም ፎረስትን በኦልድትራፎርድ ያስተናግዳል፡፡

 

Exit mobile version